Skip to main content

ስለ ኮሚሽኑ

የክልላችንን የኢኮኖሚ ዕድገት በላቀ ደረጃ ለማፋጠን ይቻል ዘንድ የአስፈፃሚ አካላት አደረጃጀት የተልዕኳቸውን ስፋትና ተቀራራቢነት መሰረት ባደረገ መልኩ እንደገና ለመወሰን በፀደቀው በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሕገ መንግስት አንቀፅ 55 ንዑስ አንቀፅ 3 በታወጀው መሰረተ በተዘጋጀ የተሻሻለው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግሥት የአስፈፃሚ አካላትን ሥልጣንና ተግባር መወሰኛ አዋጅ ቁጥር 199/2015 ዓ/ም ክፍል 5 ተራ ቁጥር 13(13) መሰረት ተጠሪነቱ ለክልሉ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሆኖ እንደተደራጀ ተደንግጓል፡፡ ይህንንም አዋጅ ተከትሎ ሙስናና ብልሹ አሰራር የክልላችንን ብሎም የሀገራችንን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ልማትን የሚያደናቅፍ ድርጊት በመሆኑ የፀረ-ሙስና ትግሉን የሚያስተባብር ተቋም በሕግ ማቋቋም አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ በሃገራችን ብሎም በክልላችን የተጀመረውን የልማት፣ የሠላም እና ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ቀጣይነት ያለው እንዲሆን ሙስናና ብልሹ አሰራርን መከላከል እንዲሁም መልካም ስነ-ምግባር የተገነባ፣ ሙስናን የሚፀየፍ እና በፅናት የሚታገል ህብረተሰብ በመገንባት የፀረ-ሙስና ትግሉን ማጠናከር እንደሚገባ በመታመኑ በአዋጅ ቁጥር 4/2016 የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት የስ-ምግባርና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን በሚል ስያሜ ተቋቁሟል::